Sunday, December 24, 2017

"Christmas"/ገና/የኢየሱስን ክርስቶስ ልደት ላንተ ምንድነው??

       
//መጽሐፈ አስቴር 9:21-22
በየዓመቱም አዳር በሚባለው ወር አሥራ አራተኛውና አሥራ አምስተኛው ቀን፥
አይሁድ ከጠላቶቻቸው ዕረፍትን ያገኙበት ቀን፥ ወሩም ከኀዘን ወደ ደስታ ከልቅሶም ወደ መልካም ቀን የተለወጠበት ወር ሆኖ ይጠብቁት ዘንድ፥ የግብዣና የደስታም ቀንእርስ በርሳቸውም ስጦታ የሚሰጣጡበትና ለድሆች ስጦታ የሚሰጡበት ቀን ያደርጉት ዘንድ አዘዛቸው።//


[26 ስለዚህም እነዚህ ቀኖች እንደ ፉር ስም ፉሪም ተባሉ] በአስቴርና በ እነ መርዶኪዎስ ዘመን የነበሩ አይሁዳውያን የፉሪም በአል ምንድነው ብለን ብንጠይቃቸው
የሚሉት ብዙ አላቸው.....እንደ ሜዶንና እንደፋርስ የጸና የንጉስ አዋጅ የሞት አዋጅ ታውጆባቸው ሳለ እግዚሃብሄር የተመረጠ ህዝቡን ለማዳን ለአስቴርና መርዶኪዎስ
በኩል ሞገስ ሆናቸው ህዝቡን ለማዳን ንጉሱ ያወጣውን ህግ አላሻረም የሞት አዋጅ እንደታወጀ ህጉ ሳይሻር ይልቁኑ ለየት ያለ የተሻለ ነገር ሆነ ይኽውም
የአይሁድ ህዝብ ሁሉ እራሱን መከላከል እንዲሁም ጠላቱን ማጥፋት የሚያስችል መብት የሚያጎናጽፍ ህግ ወጣ በየአውራጃውም እስከ ግዛቱ መጨረሻ ታወጀ


//መጽሐፈ አስቴር 8:11-13
በዚያም ደብዳቤ በከተሞቹ ሁሉ የሚኖሩት አይሁድ እንዲሰበሰቡ፥ ለሕይወታቸውም እንዲቆሙ፥ በጥል የሚነሡባቸውን የሕዝቡንና የአገሩን ሠራዊት ሁሉ ከሕፃናቶቻቸውና ከሴቶቻቸው ጋር እንዲያጠፉና እንዲገድሉ እንዲደመስሱም፥ ምርኮአቸውንም እንዲዘርፉ ንጉሡ ፈቀደላቸው።
ይህም አዳር በሚባለው በአሥራ ሁለተኛው ወር በአሥራ ሦስተኛው ቀን በንጉሡ በአርጤክስስ አገሮች ሁሉ በአንድ ቀን እንዲሆን ነው።
አይሁድም ጠላቶቻቸውን እንዲበቀሉ በዚያ ቀን ይዘጋጁ ዘንድ የደብዳቤው ቅጅ በየአገሩ ላሉ አሕዛብ ሁሉ ታወጀ።//


በአዲስ ኪዳን ለኛ የሆነው ግን ለየት ይላል.........በአዳም ሃጥያት/አለመታዘዝ ሞት ወደ አለም እንደገባ እናም የዚህ የሞት አዋጅ ሰለባዎች ሆነን ሳለ ....የሙሴ ህግ
ከሃጥያት ከሞት አላዳነንም ወይም ለነአስቴር እንደሆነው የተሻለ ህግ እራስን መከላከል የሚያስችል አዋጅ አልታወጀም ምክንያቱም ሃጥያትም መከላከል በስጋ አይቻልም ህግን በመጠበቅ መጽደቅ አልተቻለም ይልቁንም ህግ የባሰውኑ ሃጥያተኛ እንደሆንን ብቻ ነው የሚነግረ.....ይልቁኑ እግዚሃብሄር ወልድ መድሃኒያለም ሆኖ
እራሱን ለ እኛ ለመስጠት ህይወቱን ስለ ሃጥያታችን ቅጣት ሞት የኛን ሞት ለመሞት ሰው ሆኖ ወደ ምድር መጣ ...............ስለዚህ የክርስቶስ ልደት አመት በአል ወይም ሆሊ ደይ አይደለም............የጠፋውን የሰው ልጅ ለማዳን ክርስቶስ ክብሩን ትቶ እንደ ሰው ሆኖ ለአዳም ዘር ለመሞት ፈቃደኛ ሆኖ ወደ ምድር መጥቶ ከድንግል ማርያም የተወለደበት ቀን ነው.........


//የዮሐንስ ወንጌል 8:3-5
ጻፎችና ፈሪሳውያንም በምንዝር የተያዘችን ሴት ወደ እርሱ አመጡ በመካከልም እርሱዋን አቁመው፦
መምህር ሆይ፥ ይህች ሴት ስታመነዝር ተገኝታ ተያዘች።
ሙሴም እንደነዚህ ያሉት እንዲወገሩ በሕግ አዘዘን፤ አንተስ ስለ እርስዋ ምን ትላለህ? አሉት።//

ይቺ ስታመነዝር የተያዘችው እየሱስ ከሞት ያስመለጣት ሴት ዛሬ ብትኖር የኢየሱስን ልደት እንዴት ታከብረው ይሆን??

//የማቴዎስ ወንጌል 8:28
ወደ ማዶም ወደ ጌርጋሴኖን አገር በመጣ ጊዜ፥ አጋንንት ያደሩባቸው ሁለት ሰዎች ከመቃብር ወጥተው ተገናኙት፤ እነርሱም ሰው በዚያ መንገድ ማለፍ እስኪሳነው ድረስ እጅግ ክፉዎች ነበሩ።//


በአጋንንት እስራት ተይዘው የነበሩት እነዚህ ሰዎች በዚህ ዘመን ቢኖሩ የክርስቶስን ልደት እንዴት ያከብሩ ነበር???



እናንተ የኢየሱስን ልደት እንዴት እያከበራችሁት ነው?????



//ትንቢተ ኢሳይያስ 9:2
በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን አየ፤ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው።//




Friday, December 15, 2017

የእግዚሃብሄርን ጦርነት ብቻ ተዋጋ


  12/15/2017  0400

//1 ሳሙኤል 29:8-9
ዳዊትም አንኩስን፦ ምን አድርጌአለሁ? ሄጄስ ከጌታዬ ከንጉሡ ጠላቶች ጋር እንዳልዋጋ፥ በፊትህ ከተቀመጥሁ ጀምሬ እስከ ዛሬ ድረስ በእኔ በባሪያህ ምን አግኝተህብኛል? አለው።
አንኩስም መልሶ ዳዊትን፦ እንደ አምላክ መልእክተኛ በዓይኔ ፊት መልካም እንደ ሆንህ አውቃለሁ፤ ነገር ግን የፍልስጥኤማውያን አለቆች፦ ከእኛ ጋር ወደ ሰልፍ አይወጣም አሉ።አሁንም አንተ ከአንተም ጋር የመጡ የጌታህ ባሪያዎች ማልዳችሁ ተነሡ፤ ሲነጋም ተነሥታችሁ ሂዱ አለው።//

ዳዊት ከ ሳኦል ማሳደድ ለማምለጥ ወደ ፍልስጤማውያን ምድር በመሄድ አንኩስ የተባለው የጌት ንጉስ መኖሪያ ሰጥቶት ዳዊትና አብረውት ያሉት 600 ተከታዮቹ/ሰራዊት ለ 1 አመት ከ 4 ወር ኖረዋል::

ፍልስጤማውያን እስራእኤላውያን ለመውጋት በሚዘጋጁበት ጊዜ ዳዊትም አብሯቸው ለመዋጋት እንዲወጣ ንጉስ አንኩስን ሲጠይቅ ይታያል
ዳዊት እስራእኤላውያን ከዚህ በፊት ወደጦርነት ከመውጣታቸው በፊት እግዚሃብሄርን እንደሚጠይቁት በእግዚሃብሄር ፊት ሆኖ ስለጦርነቱ አብሯቸው መውጣት አለመውጣ እንዳለበት አልጠየቀም ይልቁንም በስጋዊ አስተሳሰብ ምናልባትም የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው በሚል አስተሳሰብ ሌሎች አረማውያን እንደሚያደርጉት በማሰብ የራሱን ወገኖች በምውጋት ታሪካዊ ስህተት ለመስራት ሲዘጋጅ እናያለን:: እግዚሃብሄር ግን የምህረት አምላክ ስለሆነ ዳዊት እንዳሰበው አልሆነም የፍልስጤማውያን አለቆች ከጠላታቸው ጋር ወግኖ ይወጋናል  ብለው ፈርተው አብሯቸው እንዳይወጣ ከለከሉት::

ስንት ግዜ በስጋዊ አስተሳሰብ በመነዳት የእግዚሃብሄርን ወገን በድዬ ይሆን እግዚሃብሄ ምህረቱን ይላክልኝ በእግዚሃብሄር ፊት ሆነን ያልተቀበልነው ምሪት ሆነ ስራ በስጋ ያሰብነው አብዛኝው ከውጤታማነቱ ይልቅ የሚያስከትለው ኮላቶራል ዳሜጅ ከፍተኛ ነው::በተለይ በህይወቴ በኢትዮጲያን የፖለቲካ ትኩሳት ምክንያት እንዲሁም ጌታን ከማያውቁ ሰዎች ጋር ከሚፈጠረው ጉንጭ አልፋ ክርክር እንዲሁም በመሳሰሉት መንፈስን በማጥፋት ከከፍታዬ ወርጄ ብዙ ግዜ የራሴን የስጋ ጦርነት ስዋጋ አገኘዋለሁ ...

ይህ ሁሉ የሚሆነው ተዘናግቶ በመቀመጥ በስንፍና ጠላት ዲያቢሎስ ሁልጊዜ እኛን እንደሚዞር ቀዳዳ ምክንያት እንደሚፈልግ ካለማስተዋል ነው::

እግዚሃብሄር ዳዊትን ወደ ትራክ ለመመለስ ታሪካዊ ስህተት ያለበት የተሳሳተ ጦርነት እንዳይሄድ ከከለከለው በኋላ ትክክለኛ አሳይመንት የቤት ስራ ሰጠው
የእግዚሃብሄር አላማ የህዝቡ ጠላቶች አማሌቃውያን ፈጽመው እንዲጠፊ ነው  ስለሆነም ዳዊት ፍልስጤማውያን አብሯቸው እንዳይወጣ ከከለከሉት በኋላ ወደ ሰፈር ሲመለስ አማሌቃውያን ጺቅላን ወግተው አቃጥለው በዛ የቀሩትም ምስቶቻቸውን እና ሽማግሌዎችን ማርከው ወስደዋል በዚህ ጊዜ እንደባለፈው እግዚሃብሄርን ሳይጠይቅ በፍጥነት አልወሰነም ምንም እንኳ የገዛ ሚስቶቹ እራሱ ቢማረኩም ከተማዋ እየነደደች ብትሆንም እጅግ አሳዛኝ ሁኔታ ቢሆንም አብረውት የነበሩት ሊወግሩት እስኪመካከሩ ድረስ የነገሩ ሁኔታ አስጨናቂ ቢሆንም   በስጋዊ ቁጣ ንዴት በደም ፍላት እየሮጠው ወደ ውግያ አልወጣም ይልቁንም
መጽሃፉ የሚለው **1ሳሙ30:6 ...ዳዊት ግን በአምላኩ በእግዚአብሔር ልቡን አበረታ።**.... ወደ እግዚሃብሄር በመቅረብም ልከተላቸውን ልውጣን ብሎ ጠየቀ እግዚሃብሄርም አብሮት ወጣ ምርኮም ሰጠው::
የእግዚሃንሄርን ጦርነት ተዋጋ እግዚሃብሄርም ድልን ሰጠው::



Saturday, December 9, 2017

መንፈስ ቅዱስ

መንፈስ ቅዱስ
ነገስት 6:34

የእግዚአብሔርም መንፈስ በጌዴዎን ገባበት፥ እርሱም ቀንደ መለከቱን ነፋ፤ የአቢዔዝርም ሰዎች ተጠርተው በኋላው ተከተሉት
ወደ ምናሴም ነገድ ሁሉ መልክተኞችን ሰደደ፤ እነርሱም ደግሞ ተጠርተው በኋላው ተከተሉት፤ መልክተኞችንም ወደ አሴርና ወደ ዛብሎን ወደ ንፍታሌምም ሰደደ፥ እነርሱም ሊገናኙአቸው ወጡ።
ይህ ከወገኑ ከሁሉ ይልቅ የተጠቃ(ምናሴ) ከቤተሰቡ የሁሉ ታናሽ የ እለት ስራውን እርሻውን እራሱ ተደብቆ በፍርሃት የሚሰራ ሰው.....የንግስና ዘር ከነገዱ የሌለ ስለ ጦር አመራር የማያውቅ ተራ ገበሬ እንዴት...የአቢዔዝር ሰዎች የምናሴም ነገድ ሰውች የአሴር የዛብሎን ና የንፍታሌም ሰዎች ሁሉ ከኋላው ማስከተል እንዴት ቻለ
እግዚሃብሄር እራሱ ተገልጦለት አንተ ጽኑ ሃያል ሰው ብሎት እንኳ የአባቱን የሰፈሩን የበአል መሰዊያ ለማፍረስ ከፍርሃቱ እተነሳ በሌሊት ሰው እንዳያየው ተደብቆ ነበር ያፈረሰው
የሚገርመው የሰፈሩ ሰዎች ሊገሉት ሲመጡ እራሱን እና ድርጊቱ ለመከላከል በክርክርም ለማሳመን ስለፈራ ተደብቆ እያለ የተሟገተለት የበአል አምላኪ የሆነው የበአል መሰዊያው ባለቤት አባቱ(ኢዩአስ) ነበር::ስለ እግዚሃብሄር ሃያልነት ብርታት እግዚሃብሄር የተገለጠለት እያለ ጣኦት አምላኪ የተሻለ መልስ የተሻለ ተሟጋች ሲሆን አይገርምም

ሃዋርያትን እራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ በተግባር;አብሮ በመጸለይ;ለብቻውም በመጸለይ; በሚታይ ህይወት ;በቃል;በምሳሌ ;በስልጣን ;በድንቅ ;በምልክቶች ከ3 አመት በላይ አስተምሯቸው የጭንቅ ጊዜ ሲመጣ አፈገፈጉ በተለይም ጴጥሮስ እነዚህ ሁሉ ቢክዱ አብሬህ እስከ መጨረሻው አልለይህም ያለው በአንድ ተራ ሰው ፊት አላቀውም አለ::
//ዩሃ 16:12
የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም።
ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል።
እርሱ ያከብረኛል፥ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና።
//
ይሄ የ እውነት መንፈስ ይሄ አጽናኝ ይሄ ሃይል በመጣና በነካው ጊዜ ጊዜ ግን ጴጥሮስ አይደለም በአንድ ባልተማረች ገረድ ፊት እንዳልተርበተበተ ከአለም ዙሪያ ከመጡ የተለያየ እውቀትና የተለያየ ቋንቋ ባላቸው ሰዎች ፊት ለፊት ቆሞ በድፍረት ስለ እኢየሱስ ለመናገር ደፈረ ሃይል አገኘ ጥበብ አገኘ ሞገስ አገኘ መደመጥ አገኘ መፈራት አገኘ....
ወደ ጌዲዮን ስንመለስ ተመሳሳይ ነገር ነው የሆነው እስራኤልን እንዲታደግ ተመርጦ እግዚሃብሄር አንተ ጽኑ ሃያል ሰው ብሎ ያደፋፈረው የተናገርው ነገር ግን በሰፈሩ በቤቱ የእግዚሃብሄርን ስራ ለመስራት ለመናገር ሲፈራ ሲደበቅ የምናየው ጌዲዮን የእግዚሃብሄር መንፈስ ሲገባበት ግን ልዩ ሰው ሆነ በአደባባይ መውጣት ደፈረ ቀንደ-መለከት አነሳ እንደ ንጉስ አገርን ለመታደግ አገራዊ ጥሪ ለማወጅ ተነሳ መለከት ነፋ ከሁሉ ታናሽ የነበረው በእግዚሃብሄር መንፈስ ከሁሉ ቀዳሚ መሪ ታዳጊ ሆኖ የአቢዔዝር ሰዎች የምናሴም ነገድ ሰውች የአሴር የዛብሎን ና የንፍታሌም ሰዎች እነዚህን ሁሉ ከኋላው ማሰለፍ ቻለ::


የእግዚሃብሄርን የመንግስቱን ወንጌል ለአንድ ለተራ ሰው እንኳ ማድረስ አይቻልም በራሳችን እውቀት ጥበብ አይደለም ለሌላ ሰው እኛም ትላንት በተገለጸልን እውቀት መዳን ብርሃን መጽናት አንችልም ሃዋሪያቱ አልቻሉም ጴጥሮስ ህያው ምስክር ነው ነገር ግን የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ከራሳችን ተርፈን ለጎረቤት ለአለም መትረፍ ሰዎችን ሁሉ ከኋላችን ማሰለፍ ሞገስ ጥበብ ሃይል ይሆንልናል ይበዛልናል::


መገኘትህን አትውሰድብኝ ......ያለው ዳዊት ምንኛ መንፈስ ቅዱስ ከእስትንፋስ ይልቅ የሚቀርብ እንደሆነ የገባው የተረዳ ከሚተነፍሰው አየር የበለጠ አስፈላጊ እንደሆነ የተረዳ .........በብሉይ ኪዳን ዘመን የነበረ ነገር ግን ከባለአምሳ በኋላ እንዳለው ዘመን እንደኖሩት እንደ አዲስ ኪዳን ኑሮ የኖረ የሚገርም ዳዊት

Tuesday, November 21, 2017

Dr. Abiy Ahmed


በቅርብ ግዜ እየታዩ ካሉ መሪዎች ውስጥ ለማ መገርሳ እና አቢይ አህመድ,,, //ከናዝሬት/Adama መልካም ነገር ሊወጣ ይችላልን?? ያስብላሉ አዎ መጣችሁ ይሄን ቪዲዮ እዩ!!//


መሪ(Leader) ወይስ ካድሬ


አንድ ፖለቲከኛ ካድሬ ወይም መሪ መሆኑም ለማወቅ ቀላል ዘዴዎች:

ሰው በኃይሉ አይበረታምና

የዮሐንስ ወንጌል 1:46
//ፊልጶስ ናትናኤልን አግኝቶ፦ ሙሴ በሕግ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል አለው። ናትናኤልም፦ ከናዝሬት መልካም ነገር ሊወጣ ይችላልን? አለው። ፊልጶስ፦ መጥተህ እይ አለው።//